Your browser does not support HTML5 video.
ሰብአዊ መብቶች ባህል የሆኑባት ኢትዮጵያን ማየት
የሚካሄድበት ቀን በቅርቡ ይፋ ይሆናል
የኢትዮጵያ ሰብአዊ መብቶች ኮሚሽን (ኢሰመኮ) በፌዴራል ሕገ መንግሥቱ መሠረት ነጻ ፌዴራላዊ መንግሥት አካል ሆኖ የተቋቋመና ለሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ተጠሪ የሆነ ለሰብአዊ መብቶች መስፋፋት፣ መከበር እና ጥበቃ የሚሠራ ብሔራዊ የሰብአዊ መብቶች ተቋም ነው፡፡ (የኢፌዴሪ ሕገ መንግሥት አንቀጽ 55/14 እና አዋጅ ቁጥር 210/1992 በአዋጅ ቁጥር 1224/2012 እንደተሻሻለው)
በኢትዮጵያ ሰብአዊ መብቶች ኮሚሽን (ኢሰመኮ) አዘጋጅነት ለ5ኛ ጊዜ የሚካሄደው የሰብአዊ መብቶች ፊልም ፌስቲቫል በኢሰመኮ የ2017 በጀት ዓመት የሰብአዊ መብቶች ሁኔታ ዓመታዊ ሪፖርት በከፍተኛ ደረጃ አሳሳቢ በመሆን ከተለዩት ጉዳዮች መካከል በትምህርት የማግኘት መብት እና በነጻነትት መብት ዙሪያ ያተኩራል።
በ5ኛው ዙር የፊልም ፌስቲቫል በተለያዩ ከተሞች በሚዘጋጁ መርኃ ግብሮች ላይ ለዕይታ የሚቀርቡ የፎቶግራፍ እና የአጫጭር ፊልሞች ውድድሮች አዘጋጅቷል
በኢሰመኮ የ2017 በጀት ዓመት የሰብአዊ መብቶች ሁኔታ ዓመታዊ ሪፖርት በከፍተኛ ደረጃ አሳሳቢ በመሆን ከተለዩት ጉዳዮች መካከል በነጻነት መብት እና በትምህርት መብት ዙሪያ የሚያተኩር ይሆናል
ለዚህ ሂደት የኪነጥበብ ሥራዎቹን የቴክኒክ መስፈርት የሚገመግሙ በተለያዩ የሰብአዊ መብቶች ዘርፎች የሚሠሩ ባለሙያዎች እንዲሁም የኢሰመኮ የሚድያ እና ኮሙኒኬሽን ሥራ ክፍል ባለሙያዎች የተካተቱበት ፓነል ይቋቋማሉ
ከአንደኛ እስከ ሦስተኛ ደረጃ የተመደቡ የፎቶግራፍ እና የአጫጭር ፊልሞች እንደየደረጃቸው እና እንደመወዳደሪያ ዘርፋቸው ከ25 ሺህ እስከ 125 ሺህ የገንዘብ ሽልማት (በኢትዮጵያ ብር) የሚያገኙ ይሆናል
የነጻነት መብት በዓለም አቀፍ የሰብአዊ መብቶች ስምምነቶች የሲቪል እና የፖለቲካ መብቶች ተብለው ከሚመደቡት መብቶች አንዱ ነው።
ማንኛውም ሰው ትምህርት የማግኘት መብት ያለው ሲሆን፣ በዓለም አቀፍ ስምምነቶች ኢኮኖሚያዊ፣ ማኅበራዊ እና የባህል መብቶች በመባል ከተለዩት መብቶች መካከል አንዱ ነው
በኢሰመኮ አዘጋጅነት ለሚካሄደው 5ኛ ዙር ዓመታዊ የሰብአዊ መብቶች ፊልም ፌስቲቫል የሚቀርቡየኪነ ጥበብ ሥራዎች ውድድር የተሳትፎ ቅጽ
የኢሰመኮ 5ኛ ዙር የሰብአዊ መብቶች ፊልም ፌስቲቫል የፎቶግራፍ እና የአጫጭር ፊልሞች ውድድር አጠቃላይ የውድድር መርሖች እና ደንቦች
ስለ ውድድሮቹ ዝርዝር መረጃ